Quran Apps in many lanuages:

Surah Al-Araf Ayahs #123 Translated in Amharic

فَغُلِبُوا هُنَالِكَ وَانْقَلَبُوا صَاغِرِينَ
እዚያ ዘንድ ተሸነፉም፡፡ ወራዶችም ኾነው ተመለሱ፡፡
وَأُلْقِيَ السَّحَرَةُ سَاجِدِينَ
ድግምተኞቹም ሰጋጆች ኾነው ወደቁ፡፡
قَالُوا آمَنَّا بِرَبِّ الْعَالَمِينَ
አሉ፡- «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡»
رَبِّ مُوسَىٰ وَهَارُونَ
«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»
قَالَ فِرْعَوْنُ آمَنْتُمْ بِهِ قَبْلَ أَنْ آذَنَ لَكُمْ ۖ إِنَّ هَٰذَا لَمَكْرٌ مَكَرْتُمُوهُ فِي الْمَدِينَةِ لِتُخْرِجُوا مِنْهَا أَهْلَهَا ۖ فَسَوْفَ تَعْلَمُونَ
ፈርዖን አለ፡- «እኔ ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት በእርሱ አመናችሁን ይህ በከተማይቱ ውስጥ ሰዎቿን ከእርሷ ለማውጣት በእርግጥ የተስማማችሁበት ተንኮል ነው፡፡ ወደፊትም (የሚደርስባችሁን) ታውቃላችሁ፡፡»

Choose other languages: