Quran Apps in many lanuages:

Surah Al-Araf Ayahs #125 Translated in Amharic

قَالُوا آمَنَّا بِرَبِّ الْعَالَمِينَ
አሉ፡- «በዓለማት ጌታ አመንን፡፡»
رَبِّ مُوسَىٰ وَهَارُونَ
«በሙሳና በሃሩን ጌታ፡፡»
قَالَ فِرْعَوْنُ آمَنْتُمْ بِهِ قَبْلَ أَنْ آذَنَ لَكُمْ ۖ إِنَّ هَٰذَا لَمَكْرٌ مَكَرْتُمُوهُ فِي الْمَدِينَةِ لِتُخْرِجُوا مِنْهَا أَهْلَهَا ۖ فَسَوْفَ تَعْلَمُونَ
ፈርዖን አለ፡- «እኔ ለእናንተ ሳልፈቅድላችሁ በፊት በእርሱ አመናችሁን ይህ በከተማይቱ ውስጥ ሰዎቿን ከእርሷ ለማውጣት በእርግጥ የተስማማችሁበት ተንኮል ነው፡፡ ወደፊትም (የሚደርስባችሁን) ታውቃላችሁ፡፡»
لَأُقَطِّعَنَّ أَيْدِيَكُمْ وَأَرْجُلَكُمْ مِنْ خِلَافٍ ثُمَّ لَأُصَلِّبَنَّكُمْ أَجْمَعِينَ
«እጆቻችሁንና እግሮቻችሁን በማፈራረቅ በእርግጥ እቆራርጣለሁ፡፡ ከዚያም ሁላችሁንም በእርግጥ እሰቅላችኋለሁ፡፡»
قَالُوا إِنَّا إِلَىٰ رَبِّنَا مُنْقَلِبُونَ
አሉ፡- «እኛ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፡፡»

Choose other languages: